በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የጀማሪ ስራ ፈጠራ(ስታርታፕ) ሥነ-ምህዳር ማጠናከር የሚያስችል ውይይት ተደረገ - ኢዜአ አማርኛ
በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የጀማሪ ስራ ፈጠራ(ስታርታፕ) ሥነ-ምህዳር ማጠናከር የሚያስችል ውይይት ተደረገ

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 16/2017(ኢዜአ)፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ ባዳዳ(ዶ/ር) ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሉዊስ አንቶኒ ጋር በኢትዮጵያ ያለውን የጀማሪ ስራ ፈጠራ(ስታርታፕ) ሥነ-ምህዳር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
የፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ ከአውሮፓ ህብረት እና ኤክስፐርቲስ ፍራንስ ጋር በመተባበር የስታርታፕ ሥነ-ምህዳሩን ለማጠናከር 10 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ለማድረግ እንደተዘጋጀም ተገልጿል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ ባዳዳ(ዶ/ር) ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሉዊስ አንቶኒ ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የጀማሪ ስራ ፈጠራ (ስታርታፕ) ሥነ-ምህዳር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።
የፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ ከአውሮፓ ህብረት እና ኤክስፐርቲስ ፍራንስ ጋር በመተባበር የስታርታፕ ሥነ-ምህዳሩን ለማጠናከር 10 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ለማድረግ እየተዘጋጀ መሆኑ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል።
ይህም ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረውንና በቅርቡ ወደ ስራ የሚገባውን የስታርታፕ አዋጅ ወደ ተግባር ለማሸጋገር እንደሚረዳ የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
በተጨማሪም የስታርታፕ ኢንኩቤሽን ሞዴሎችን ማሻሻል እና የስታርታፖች አቅም ማጠንከርና የፈንድ ምንጮችን ለመጨመር መግባባት ላይ ተደርሷል።
ሚኒስትር ዴኤታው እና ዳይሬክተሩ በኢትዮጵያ ያሉ ስታርታፖች በአውሮፓና ፈረንሳይ የስታርታፕ ስነምህዳር እንቅስቃሴዎች ላይ ተሳትፎ የሚያደርጉብት ዕድል በሚፈጠርበት ሁኔታ ላይ በጋራ እንደሚሰሩም ገልጸዋል።