የዓለም የአብራሪዎች ቀን እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 18/2017(ኢዜአ)፦ዓለም አቀፉ የአብራሪዎች ቀን (World Pilots’ Day) ዛሬ እየተከበረ ይገኛል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት የዛሬው ቀን የአየር መንገዱ የስኬት እና የጀግንነት ተምሳሌት ለሆኑት አብራሪዎች ክብር የምንሰጠበት ነው ብሏል።

አብራሪዎች በክህሎታቸው፣ በታታሪነታቸው እና በጠንካራ የጸና መንፈስ የአፍሪካን ህልሞች ወደ ተለያዩ የዓለም ክፍሎች ይዞ በመጓዝ ሀገራትን፣ ባህሎች እና እድሎችን በማስተሳሰር ቁልፍ ሚና እየተወጡ ነው ብሏል።

ዛሬም ሁልጊዜም እናከብራችኋለን ሲል ገልጿል አየር መንገዱ ባስተላለፈው መልዕክት።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም